Featured Causes

ልጆች ልጆች የዛሬ አበባዎች የነገ ፍሬዎች

ከምንም በላይ የልጆች መጎሳቆል ፣መሰደድ ፣መፈናቀል ፣አውላላ
ሜዳ ላይ ከመጣል የሚያክል ህመም የለም ። የአማራ ህጻናቶች
በማንነታችው ሳቢያ ለሞት ፣ልስደት ፣ለወላጅ አልባነት ተዳርገዋል
።በቅርብ በትግራይ እና በመንግስት መካከል በተደረገው
ጦርነት ሳቢያ ደሞ በክልል ውስጥ የሚኖሩትም ህጻናት
ከክልል ውጭ ከመጡ ህጻናት እኩል ቤት አልባ ፣ወላጅ
አልባ ሆነው በየ መጠለያው ተጥለው ፣ተፈናቅለው ይገኛሉ
።የነገ ፍሬዎቻችንን ለማዳን የእርሶ አስተዋጽዕ እጅግ ስለሚያስፈልግን በሚችሉት አቅም ልጆቻችን እንታደግ በማለት አለማቀፍ ቤተ አማራ ወሎ ጥሪዉን አቅርቦሎታል ።

ልጅ ያላባት ማሳደግ ከባድ ነው በተለይ ተፈናቅሎ ቤት አልባ ሆኖ

አማራዊ እህቶቻችን በተለያየ መልኩ ለዚህ አይነቱ ችግር በከፍተኛ ቁጥር ተጋልጠዋል ።በማንነት ከመገደል እስከ ጦርነት ሰለባ የመሆንና ልጆችን የብቸኛ ሀላፊዎች ብቸኛ ወላጅ እንዲሆኑ ተፈጥሮም ሰው ሰራሽ ችግርም አስገድዷችዋል።

ብዙዎቻችን አባት ፣እናት ተክዘው ተስፋ ቆርጠው ስናይ ልባችን ይሰበራ

ፎቶ ሺ ቃላት ይናገራል ይባላል። ብዙ አማራ አባወራዎች በመጦሪያችው ዘመን ንብረታችው ወድሞ ልጆቻችው ለአንድም
ለሌላ ሰለባ ሆነውባችው ጧሪ አልባ ወገን አልባ
ሆነው ተክዘው ተቆራምተው ከማየትበላይ
የሚያም ነገር የለም ። ላለፊት 35 አመታት
በአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረው ችግር ፣መጎሳቆል
፣መፈናቀል ዛሬም ላይ ጦርነቱ ተደምሮበት
ከፍተኛ ቁጥር ያላችው አማራ አዛዋንቶች በየመጠለያ
ቦታ ተጥለው ይገኛሉ ።መቼም ከወላጅ ያልተፈጠረ የለም ።
አመት ባዕል ሲደርስ ከወላጅ ጋር ማሳለፍ ወላጅ ደስ እንዲለው ማድረግ መመኘት የሁላችንም ፍላጎት ነው። እስቲ የምንችለውን አድርገን ቢያንስ በቀን አንድ ጊዜ እንዲመገቡ እንርዳችው !

How you’re changing children’s lives

Health

እርሶ የሚሰጡት ምንም አይነት ስጦታ አይናቅም።ምንም እንኳን ለተሰደዱ ፣ለተፈናቀሉ ቤተሰቦች የመልሶ ማቋቋም ቤት መስራት ባንችልም ፣ነገር ግን እርሶ በሚሰጡን ምንም አይነት ድጋፍ ፥ ልጅቾ በቀን አንድ ጊዜ እንዲመገቡ ለማድረግ ያስችለናል። ከተፈጥሮ እና ከጦርነቱ ያመጣብን ችግር በላይ አያሌ ብዙ ህጻናቶች ለማለኔሪሽመት አደጋ ተጋልጠዋል ።

Education

Bete Amhara Wollo Books for Education

አለማቀፍ ቤተ አማሀራ ድርጅት ፣ለምግብ እርዳታ ከማሰባሰብ ባሻገር  ፣

ለልጆች መማሪያ የሚሆን መጸሀፍቶችንም አበርክቷል ።ከናንተ ከደጋፊዎቻችን ጋር በመተባበር ፥ለልጆች የሚጠቅም የመማሪያ ቁሳቁሶችን ፣ደብተሮችን ለማቅረብ ከፍተኛ  ስራ እየሰራ ይገኛል ።ምንም እንኳን ልጆቻችን ተሰደው ፣ቤት አልባ ሆነው በመጠላይ ቢገኙም ፣ የትምህርት ብቃተ ህሊናችው እንዲጎለበት ለማድረግ  የበኩላችንን ለማድረግ ግድ ይለናል ። 

Our Volunteers

Teferi Abegaz

Chairman

Seada Ali

Public affairs

Mohammed Ali

Vice Chairman

Kalkidan

Secretory

Testimonials

Lorem ipsum dolor sit amet
የቤተ አማራ ወሎ አለማቀፍ ድርጅት መስራቾች እና አባላቶችን ላመስግን እወዳለሁ ። ወገኖቻችን አውላላ ሜዳ ላይ ተጥለው ተርበው ማየት አንሻም በማለት ያላችውንም ሰጥተው ፣ሌሎች ወገኖችን በመለመን ለወገናችው አቅማችውን በሚችለው መጠን እየረዱ ይገኛሉ ። ይሄ ትልቅ ስራ እና በጎ አድራጎት ሊበረታታ እና ሊደገፍ ይገባዋል ።
እስክንደር ተፈሪ
ቤተ አማራ ወሎ አለማቀፍ ድርጅት ወገኖቹን እያስተባበረ ለወገኖቹ ደራሽነቱን አሳይቷል ። ይሄም ድርጅት ጥንካሬውን አጠናክሮ እያደረገ ካለው በጎ ስራ በተሻለ መልኩ ለመስራት ለት ከለት እየደከሙ ይገኛሉ ። እነዚህ በጎ አድራጎት ወገኖች ልንደግፋችውን እና ከጎናችው ቆመን አቅማችን የፈቀደውን ልንረዳችው ይገባናል ።
ሰላማዊት ደጀኔ
ጊዚያችውን ገንዘባችውን መስዋዕት አድርገው ለወገናችው አቅማችው በፈቀደ መልኩ የሚያደርጉትን የአለም አቀፍ ቤተ አማራ ወሎ በጎ አደራጎት ድርጅትን ላመሰገን እወዳለሁ ። በዚህ ጊዜ ወገናችን ለከፋ ችግር እና አደጋ የተጋለጠበት ጊዜ እና ዘመን ነው። እኛም በበኩላችን የቻልነውን ያህል ልንደግፍ ይገባናል።
Seada Mohammed